ዜና፡ በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን በቆጂ ከተማ የታጠቁ ሀይሎች በከፈቱት ጥቃት ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ አራት ሰዎች ተገደሉ
በቆጂ ከተማ፤ ፎቶ -ቪዚት ኦሮሚያ አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14/2015 ዓ.ም፡- የአትሌቶች መፍለቂያ በመባል የምትታወቀው በቆጂ ከተማ የታጠቁ ሀይሎች አርብ ግንቦት 11 2015 በከፈቱት ጥቃት ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ አንድ የሚኒሻ አባልና አንድ የጥበቃ ሰራተኛ በድምሩ አራት ሰዎች መግደላቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለፁ፡፡ በከተማዋ ላይ ጥቃቱ የተፈፀመው የቱርዚም