ዜና፡ ሰባት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን በኮሌራ በሽታ ሊጠቁ ይችላል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስጋቱን ገለጸ፤ እስካሁን 94 ሰዎች ሞተዋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11/2015 ዓ.ም፡- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ኦቻ ይፋ ያደረገው ሪፖርት እንደሚያመለክተው ሰባት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን የኮሌራ ወረርሽኝ ሊያጠቃቸው ይችላል ሲል ስጋቱን ገልጿል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሪፖርቱ እንዳስታወቀው ኮሌራ 94 ሰዎች ገድሏል። እስካሁን 6ሺ 157 በኮሌራ የተጠቁ ሰዎች መኖራቸውንም ጠቁሟል። ወረርሽኙ በደቡብ እና