ዜና፡ የምስራቅ አፍሪካ ወታደራዊ ተቋማት በጋራ ለመስራት ተስማሙ፣ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የፓትሮል ቅኝት ተግባራትን ለማጠናከር እንደሚሰራ አስታወቀ
ጌታሁን ፀጋዬ ሚያዚያ 10፣ 2014፣ አዲስ አበባ -የምስራቅ አፍሪካ ወታደራዊ መረጃ ተቋማት ከሚያዚያ 8 እስከ 9፣ 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገው የጋራ የውይይት መድረክ ላይ በቀጠናው ፀጥታና ደህንነት ጉዳዮች ዙርያ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስታወቀ። በምክክር መድረኩ የተሳተፉ ሀገራት ጁቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳን፣