እለታዊ ዜና፡ በመዲናዋ ከፍተኛ የውሀ እጥረት መከሰቱን የአዲስ አበባ ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ
ምስል- አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11/2014 ዓ.ም፡- በአቃቂ ከርሰ ምድር የውኃ ፕሮጀክት ውስጥ የሚገኙ አምስት የውኃ ጉድጓዶች በጎርፍና ደለል በመሞላታቸው ምክንያት በመዲናዋ ከፍተኛ የውኃ እጥረት መከሰቱን የአዲስ አበባ ከተማ ውኃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ በቀን 20 ሺሕ ሜትር ኪዮብ ውኃ የማምረት አቅም ያላቸው አምስቱ