ዜና፡ በወልቂጤ ከተማ ኮማንድ ፖሰቱን እና የክላስተር አደረጃጀትን በመቃወም ሁለተኛ ዙር የስራ ማቆም አድማ እያደረጉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ገለፁ
ምስል ማህበራዊ ድህረገፅ በብሩክ አለሙ @Birukalemu21 አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20/2014 ዓ.ም፡- በወልቂጤ ከተማ ኮማንድ ፖሰቱን እና ክላስተርን በመቃወም የሁለት ቀን ስራ የማቆም አድማ እየተደረገ መሆኑን የከተማው ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለፁ፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ የታዘዘው ኮማንድ ፖስት ህገ መንግስቱ በሚፈቅደው መሰረት ባለመሆኑ የማህበረሰቡ የመንቀሳቀስ መብቱ መታገዱን