ዜና፡ አዲስ “ቤተ ክህነት” አቋቁመናል በማለት ያሳወቁ ጳጳሳትን የተቃወሙ ሰዎችና የሃይማኖት መሪዎች ላይ የሰበዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን ኢሰመኮ አስታወቀ
አዲስ አበባ፣ ጥር 3/ 2015 ዓ.ም፡- አዲስ “ቤተ ክህነት” አቋቁመናል በማለት ያሳወቁ ጳጳሳት በአንዳንድ ቦታዎች በኃላፊዎች ድጋፍ ጭምር በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች የሚገኙ ሀገረ ስብከቶችን መያዛቸውን ተከትሎ ይህን ድርጊት በተቃወሙ ሰዎችና የሃይማኖት መሪዎች ላይ በመንግሥት የጸጥታ አባሎች በርካታ የሰበዓዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች