ዜና፡ ህወሓት የምርጫ ቦርድን ውሳኔ እንደማይቀበለው አስታወቀ፤ የትግራይ ግዜያዊ አስተዳደር በበኩሉ ውሳኔው የአስተዳደሩን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲል ገልጿል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9/2015 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በህወሓት ህጋዊ ሰውነት ዙሪያ ያስተላለፈውን ውሳኔ አስመልክቶ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) እና የትግራይ አካታች ጊዚያዊ አስተዳደር በተናጠል ውሳኔውን እንደማይቀበሉት የሚያመላክት መግለጫ አውጥተዋል። ህወሓት ባወጣው መግለጫ በቦርዱ የተሰጠው ውሳኔ ቅቡልነት የሌለው፣ በፕሪቶርያ የተደረሰው ስምምነትና ህግን መሰረት ያላደረገ ነው