ዜና፡ በኢትዮጵያ ለተረጂዎች የቀረበ እርዳታ መዘረፉ ሀገራችን ያለችበትን የከፋ የሌብነት፣ ሙስና እና ኢ-ሰብዓዊነት ደረጃ የሚያሳይ ነው ሲል ኢዜማ ገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9/2015 ዓ.ም፡- የኢትዮጵ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) መንግስት ለጋሽ ሀገራት እና ድርጅቶች ለተጎጂዎች የሚሰጥን እርዳታ ላልታለመለት አገልግሎት እያዋለው ነው በሚል እርዳታ ማቆማቸውን ተከትሎ መግለጫ አውጥቷል። መንግሥት ከታረዙ ዜጎች ጉሮሮ የሚነጥቀው ሰብዓዊ እርዳታ ሃገራችን ያለችበትን የከፋ የሌብነት፣ ሙስና እና ኢ-ሰብዓዊነት ደረጃ የሚያሳይ ነው ሲል