ዜና፡ መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ መጀመሩን አስታወቀ፤ ውሳኔውን አብን እና ባልደራስ ቢቃወሙትም ኢዜማ ግን ተቀባይነት ያለው ተግባር ነው ብሎታል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29/ 2015 ዓ.ም፡- መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ የሚያስችል አንድ ጠንካራ የተማከለ ሠራዊት ለመገንባት ሲባል የየክልሉን ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ የሚያስችላቸውን ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ መጀመሩን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ ትላንት ባወጣው መግለጫ በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የልዩ ኃይል አባላት