ዜና፡ የትግራይ ክልል መንግስት በአፍሪካ ህብረት የቀረበለትን የድርድር ግብዣ መቀበሉን ገለፆ ተጨማሪ ማብራሪያ ጠየቀ
የትግራይ ክልል ፕረዜደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤል (ፒኤችዲ)፤ ምስል- ትግራይ ሚዲያ ሀውስ በአዲስ ስታንዳርድ ሪፖርተሮች አዲስ አበባ፣ መስከረም 26/2015 ዓ.ም፡- የትግራይ ክልል መንግስት ትላንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫ በአፍሪካ ህብረት የቀረበለትን የሰላም ድርድር ግብዣ እንደተቀበለ ገልፆ፣ ነገር ግን በሰላም ውይይቱ ተጨማሪ ተሳታፊዎች፣ ታዛቢዎች ወይም ዋስትና ሰጪዎች የሚጋበዙ እንደሆነ፣ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምን አይነት ሚናዎችን ሊሰጥ እንደታሰበ እና ለተደራዳሪ ቡድኑ