ዜና፣ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንኮበርን ጨምሮ በአራት ወረዳዎች ላይ የማሽላ ጢንዚዛ ወረርሽኝ ተከሰተ
በአሰፋ ሞላ @AssefaMolla6 አዲስ አበባ፣መስከረም 24/2015 ዓ.ም፡- በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአንኮበር፣ ጣርማበር፣ ቀወት እና በረኸት ወረዳዎች የማሽላ ጢንዚዛ ወረርሽኝ መከሰቱን በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።የቀበሌና የወረዳ ባለሙያዎች ጢንዚዛው በሰብሉ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ፣ በባህላዊ ዘዴ በመልቀም፣ ማሽላውን በማወዛወዝና ጭስ በማጨስ እንዲሁም