ትንታኔ፡ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በተከሰተው ድርቅ በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ የተጠለሉ ተፈናቃዮች በቂ እና ፍትሃዊ የዕርዳታ ክፍፍል ባለመኖሩ በከፍተኛ ችግር ውስጥ መሆናቸውን ገለፁ
ቦረና ዞን ኤልወያ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች እርዳታ በመጠባበቅ ላይ እያሉ፤ ፎቶ- አዲስ ስታንዳርድ በብሩክ አለሙ @Birukalemu21 እና በመድኃኔ እቁባሚካኤል @Medihane ቦረና/አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27/2015 ዓ.ም፡- ለተከታታይ አምስት አመታት በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በተከሰተው ድርቅ ሳቢያ ሁሉንም ከብቶቻቸውንና ንብረቶቻቸውን ያጡት የዱብሉቅ ወረዳ አርብቶ አደሮች ከወረዳው የተለያዩ 13