ዜና፡ በተደጋጋሚ በሚከሰተው ድርቅ ክፉኛ መጎዳታቸውን የሶማሌ ክልል የዳዋ ዞን ነዋሪዎች ገለጹ፣ ረሃብ የሰው ህይወት መቅጠፍ ጀምሯል
በመድሃኔ እቁባሚካኤል @Medihane አዲስ አበባ፣ የካቲት 28/ 2015 ዓ.ም፡– በሶማሌ ክልል ዳዋ ዞን በተከሰተው ከፍተኛ ድርቅ በርካታ ሰዎች ተጊጂ መሆናቸውን፣ እንስሳት እየሞቱ መሆኑን፣ ወንዞችም ሆነ የውሃ ጉድጓዶች መድረቃቸውን፤ ሰዎችም መሞት መጀመራቸውም ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ ገልፁ፡፡ በዞኑ በሚገኙ አራት ወረዳዎች ሞያሌ፣ ሁዴት፣ ከደዱማ እና ሙባረክ የሚኖሩ አርብቶ አደሮች