ዜና፡ ማኅበረ ቅዱሳን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን “የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያን” ያገደው የመገናኛ ብዙኃኑን አዋጅ በጣሰ መልኩ ነው ሲል ቅሬታ አቀረበ፤ እግዱን እንዲያነሳም ጥሪ አቅርቧል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14/ 2015 ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያካሄደውን ስብሰባ የሚያውክና ህዝብን ለግጭት የሚያነሳሳ መልዕክት አሰራጭቷል፣ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን ተላልፏል በሚል እሁድ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያን በጊዜያዊነት ማገዱን ተከትሎ፤ ጣቢያው ከመገናኛ ብዙኃን አዋጅ