ዜና: የወልድያ ከተማ አስተዳደር ከ123 በላይ ተጠርጣሪ “ሰርጎ ገቦች” እና “ጸጉረ ልውጦችን” ይዞ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ
የተጠርጣሪዎች ምስል::ፎቶ: አሚኮ አዲስ አበባ፤ መስከረም 06/2015 ዓ.ም፦ የወልድያ ከተማ አስተዳደር ሰላም እና የሕዝብ ደኅንነት ጽሕፈት ቤት ሕወሃት ያሰማራቸው "ሰርጎ ገቦች" ና "ጸጉረ ልውጥ" ሲል የከሰሳቸውን ከ1 መቶ 23 በላይ ተጠርጣሪዎች ይዞ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ጽሕፈት ቤት ኅላፊ አቶ ጌታቸው ካሳው ለአሚኮ አስታወቁ
0 Comments