ዜና ትንታኔ፡ የደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ተፈታኞች በፈጠሩት ሁከት የአንድ ተማሪ ህይወት አልፏል፤ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከ12ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናው ትተው ወጥተዋል፡ ትምህርት ሚንስቴር
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በብሩክ አለሙ @Birukalemu21 አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3/2015 ዓ.ም፡- በትንትናው እለት በደብረታቦር ዩኒቨርስቲ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ሃይል በተቀላቀለበት መልኩ በፈጠሩት ሁከት የአንድ ተማሪ ህይወት ማለፉንና በፈተና አስፈጻሚዎችና በፀጥታ ሃይል ላይ ጉዳት መድረሱን ትምህርት ሚንስቴር አስታወቀ፡፡ ለፈተና ወደ ዩኒቨርሲቲ የገቡ ተማሪዎች ከትምህርት ሥርዓት ባፈነገጠ