ዜና፡ አለም አቀፉ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ ግጭትን በዘላቂነት ለማስቆም ስምምነት ላይ መደረሱን በመልካም ተቀበሉት፣ ስምምነቱ በአፋጣኝ እንዲተገበር ጥሪ አቀረቡ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25/ 2015 ዓ.ም፡- የአለም አቀፉ ማህበረሰብ አባላት እና የተለያዩ ዲፕሎማቶች በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግስት እና በሕወሓት ተወካዮች መካከል በደቡብ አፍሪካ የግጭት ማቆም ስምምነት መፈራረማቸውን በደስታ ተቀብለውታል፡፡ በአፍሪካ ህብረት መሪነት ከጥቅምት 25 ጀምሮ በፕሪቶሪያ ሲካሔድ የነበረው የሰላም ድርድር ሲጠናቀቅ ተፋላሚዎቹ ወገኖች ግጭቱን ለማቆም ረቡዕ ተስማምተዋል፡፡ የህብረቱን