ዜና፡ ከሰላም ስምምነቱ በኋላም በትግራይ ትልቁ ሆስፒታል የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት አልተቀረፈም፤ የላብራቶሪ ኬሚካል ግብእቶች እንዲቀርብለት ተማጽኗል
በምህረት ገ/ክርስቶስ @MercyG_kirstos አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 25፣ 2015 ዓ.ም፡- “የሰላም ስምምነቱ ቢደረግም የመድኃኒት አቅርቦት እጥረት አልተቀረፈም” ሲሉ የትግራይ ክልል ትልቁ የዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል ዶክተሮች ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ። ከጦርነቱ በፊት በፌደራል መንግስት ሲተዳደር የነበረው የዓይደር ሪፈራል የሆስፒታል ዶክተሮች ህይወት እድን የሆኑ የመድሃኒት ቁሳቁስ ድጋፍ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸውን የሆስፒታሉ ዋና