ዜና: ሳዑዲ አረብያ ዜጎቿ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞችን እንዲቀጥሩ ከሶስት አመታት በኋላ ፈቀደች፤ ኤጀንሲዎች የሚጠየቁት የቅጥር ክፍያ ጣሪያ እጅግ አነስተኛ መሆኑ ተገልጿል
ፎቶ ከsaudi-expatriates ድረገጽ አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5/ 2015 - የሳዑዲ አረብያ መንግስት ዜጎቹ ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞችን እንዲቀጥሩ ከሶስት አመታት በኋላ መፍቀዱን ይፋ አደረገ። በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የቤት ሰራተኛ የሚመለምሉ ኤጀንሲዎች ኢትዮጵያውያንን ሲቀጥሩ ቅጥሩን ለመፈጸም ከሳዑዲ መንግስት የሚጠየቁት የቅጥር ክፍያ ጣሪያም ተቀምጧል። በተቀመጠው የክፍያ ጣሪያ መሰረትም አንዲት ኢትዮጵያዊት