ዜና፡ ታግተው የነበሩት የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰራተኞች በክፍያ ተለቀቁ
አዲስ አበባ፣ ጥር፣24/ 2015 ዓ.ም፡- ባልታወቁ ታጣቂዎች ታግተው የነበሩት ቁጥራቸው 20 የሚሆን የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰራተኞች እያንዳንዳቸው ከ50ሺ ብር እስከ 100ሺ ብር ክፍያ ሰኞ እለት መለቀቃቸውን በጉዳይ በቂ መረጃ ያላቸው አንድ ምንጭ ለአዲስ ስታንዳርድ ተናገሩ። ክፍያውን መፈፀም ያልቻሉ ደግሞ በኋላ ላይ ለመክፈል ቃል በመግባት ተለቀዋል
0 Comments