ትንተና: – ህገ-ወጥ ግንባታ እና የቤቶች እድሳት የጀጎል ግንብን ለአደጋ እየዳረጉት ነው

በምህረት ገ/ክርስቶስ @MercyG_kirstos

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9/2015 ዓ.ም፦ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በአለም ቅርስነት ካስመዘገበቻቸዉ በርካታ ታሪካዊ ቅርሶች መካከል አንዱ የሆነዉና ከአዲስ አበባ 525 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የሐረር ከተማ የሚገኘው የጀጎል ግንብ የከፋ አደጋ አንዣቦበታል ይላሉ ነዋሪዎች፡፡

ግንቡ ከጠላት ለመከላከል ታስቦ ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን ባለው ግዜ እንደተገነባ የታሪክ ማህደራት ያሳያሉ።  ሀረር ከተማ የ82 መስጊዶች መኖሪያ በመሆኗ በአለም አቀፍ ደረጃ ቀዳሚዋ የእስልምና ቅድስት ከተማ ተደርጋ ትወሰዳለች።

ልዩ ባህላዊ ዲዛይን ያላቸው  ቤቶችን የያዘበው  የጀጎል ግንብ የከተማይቱ አስደናቂ ባህላዊ ቅርስ  ሲሆን የከተማዋ ህብረተሰብ ከግንቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ ጥቅሞችን እያገኘ እንደሆነ ይታወቃል።

 ይሁን እንጂ በግንቡ ውስጥ በመገንባት ላይ ባሉት  አዳዲስ ህገወጥ ግንባታዎች እና የቤቶች እድሳት ምክንያት  ግድቡ ባህላዊ እሴቶቹን እያጣ መምጣቱን የተለያዩ አካላት ስጋታቸውን እየገለጹ ነው።

 የሐረሪ ምክር ቤት በኦንታሪዮ እ.አ.አ. በህዳር 15 ቀን 2022 ዓም  ባወጣው መግለጫ የጀጎል ግንብ ከፍተኛ ባህላዊ ቅርጹን እያጣና እየፈራረሰ መሆኑን ገልጿል። የጀጎል ግንብን ጨምሮ ሌሎች በርካታ የሀረሪ ቅርሶች አደጋ ላይ መሆናቸውንም በመግለጫው  አስታውቋል።

ነዋሪዎች በጥንታዊቷ የሀረር ከተማ ዘመናዊ ቤቶችን ለመገንባት በሚያደርጉት እንቅስቃሴ  የከተማዋን  ባህላዊ  ቅርስነት የጠበቀ እንዳልሆነ  መግለጫው አጽንዖት ሰጥቷል።

“ቅርሶቹ  በቸልተኝነት እና በግዴለሽነት ባህላዊ ይዘታቸውን የሚያጠፋ እድሳት እየተደረገባቸው ነው። ከዚህም ባሻገር  ሆን ተብሎ በቅርሱ ላይ ውድመት  እየደረሰበት ነው”

ሐረሪ ምክር ቤት በኦንታሪዮ

ለዘመናት በከተማው ውስጥ ያለው ባህላዊ የአኗኗር ዘይቤ ለአዳዲስ ስርዓቶች መንገድ እየሰጠ በመሆኑ  በግንቡ ውስጥ የነበሩት ቤቶች ባህላዊ ቅርጻቸውን እየለቀቁ ነው። 

እስካሁን ባለው ሁኔታ  ለተፈጥሮ አካባቢ እና ለሐረር ታሪካዊ ስፍራዎች የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ ነው።  “ቅርሶቹ  በቸልተኝነት እና በግዴለሽነት ባህላዊ ይዘታቸውን የሚያጠፋ እድሳት እየተደረገባቸው ነው። ከዚህም ባሻገር  ሆን ተብሎ በቅርሱ ላይ ውድመት  እየደረሰበት ነው” ሲል ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።

 በአሁኑ ጊዜ በጀጎል ግንብ  ላይ ቀላል የማይባል  ችግሮች እያጋጠመው  መሆኑን  ነዋሪዎች እና የቅርስና ባህል  ባለስልጣናት አረጋግጠዋል።  

እንደ ባለስልጣናቱ  ገለጸ እነዚህን  ቅርሶችን አደጋ ላይ የሚጥሉ ተግባራት በመለየት  ችግሮቹን ለመቅረፍ የከተማ አስተዳደሩ እየተንቀሳቀሰ እንደሆ ጠቁመዋል።

 አቶ ተወልዳ አብዳሾ የሐረር ከተማ ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ናቸው።  በጀጎል ግንብ  ውስጥ ያልተፈቀደ ግንባታ እና የቤቶች እድሳት ቅርሱን ህልውና እያሳጣው ነው ብለዋል ።

በተለይ ደግሞ  የባህል ቅርስ ጥበቃና የሰው ህይወት ልማት አስተሳስሮ መሄድ ባለመቻሉ  የጀጎል ግንብ ባህላዊ ዲዛይን ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደ ዘመናዊ ቅርጽ  ይቀየራል  የሚል ስጋት ሰፍኗል።

የከተማው አስተዳደር ቤታቸውን የሚያሳድሱ ነዋሪዎች ቀደም ሲል የነበረውን ባህላዊ ቅርጽ ጠብቀው እንዲያሳድሱ   መግባባትን ስፈጥር  መቆየቱን   አቶ ተወለዳ ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል።

በጀጎል ግንብ ላይ ስጋት ከደገኑበት ነገሮች መካከል የባጀት እጥረት ፣ የእንከባከቤ ማነስን፣ የውሃ ቁፋሮ፣  በንፅህና አጠባበቅ እና በአረንጓዴ ቅርሶች ላይ አነስተኛ የማህበረሰብ ተሳትፎ እና ኃላፊነትን ባግባቡ ያለመወጣት   ግንቡን  ለአደጋ እየዳረጉት ካሉ  ነገሮች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው ብለዋል።

 በጀጎል ውስጥ  የሚገኙ ለመጥፋት የተቃረቡ የመኖሪያ ቤቶችን፣ አብያተ ክርስቲያናትን፣ መስጊዶችን፣ ሙዚየሞችን እና ሌሎች ታሪካዊ፣ ሃይማኖታዊ እና ጥንታዊ ቅርሶችን ለመታደግ መመሪያ መውጣቱን የገለጹት የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ በግንብ ላይ እያንዣበበ ያለውን አደጋ በመገንዘብ በሃረሪ ክልል ፕሬዝዳንት ኦርዲን በድሪ የሚመራ ግብረ ሃይል ተቋቁሟል ብለዋል።  

የኮሚቴው ዋና ተግባር በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚካሄደውን ያልተፈቀደ ግንባታ ክትትል ማድረግ፣ የሚታደሱ ቤቶች ቅርስነታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ለማገዝ እንደሆነ የተናገሩት ሃላፊው  ይህ ግን ለአንድ አካል ብቻ የሚቀር ተግባር አይደለም ይልቁንም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ቅርሳቸውን  የመጠበቅ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።  

 አቶ ተወልዳ  አያይዘውም “በዩኔስኮ የተመዘገቡትን የዓለም ቅርሶች ለመጠበቅና ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ እንቅስቃሴ አለ” ነው ያሉት። 

የጀጎል ግንብ እንደ አክሱም ወይም ላሊበላ ዓይነት  ቅርሶች  በአንድ ቦታ  አልተተከለም።  

“አሁን ያለው ትውልድ የጀጎል ግንብ ባህላዊ ባህላዊነትን ለመጠበቅ  ሀላፊነቱን እየተወጣ  አይደለም”

አቶ ተወለዳ

 ባህላዊ ይዘቱን  ተጠብቆ ለዘመናት ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ የመጣው ግንቡ ከቅርብ ግዜ ወዲህ  በአንዳንድ ማህበራዊ እና አካባቢያዊ ሁኔታዎች ምክንያት ለአደጋ ተጋልጧል።

 “አሁን ያለው ትውልድ የጀጎል ግንብ ባህላዊ ባህላዊነትን ለመጠበቅ  ሀላፊነቱን እየተወጣ አይደለም” ሲሉ አቶ ተወለዳ አክለው ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ  የጀጎል መዋቅራዊ ዲዛይንና ባህላዊ ቅርሶች ላይ ቀደም ሲል ሰጥቶት የነበረ ፈቃድ እንደገና ለማጤንና ለማስተካከል  እየሰራ ነው።

በእርግጥ የከተማ አስተዳደሩ በጁጎል ውስጥ አሮጌ ቤቶችን ማደስ ለሚፈልጉ ነዋሪዎች ፈቅዷል  ነገር ግን የድሮውን ቤት ባህላዊ መዋቅር እና ዘይቤን መጠበቅ አለባቸው። ነዋሪዎች ግን ይህንን እየተዉ ወደ ዘመናዊነት መቀየርን ይመርጣሉ።  

የከተማ አስተዳደሩ ያለፈውን ውሳኔ ገምግሞ አንዳንድ ማሻሻያዎችን በማድረግ የቅርሱን እሴትን ለማስጠበቅ የሚያግዙ ማሻሻያዎችን ማድረግ እንደሚገባ  የቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።

 ሀጂ መሀመድ ሀሺም ኡመር የሐረር ነዋሪ ናቸው። ለዓመታት ጅቦችን ለቱሪስት መስህብነት  ሲመገቡ ቆይተዋል።   ቀደም ሲል ለአዲስ ስታንዳርድ እንደገለጹት  ከተማዋ ሁሉም አፍሪካውያን የሚኮሩባት የዓለም ቅርስ ነች።

ሐጂ መሀመድ አያይዘውም “ቀድም ሲል የነበሩ እንደ  እንግዳ ተቀባይነት ፣ የግንቡም ሆነ  በውስጡ ያሉ  ቤቶች  አያያዝ በአሁኑ ጊዜ እንደቀረ ገልጸዋል።  

ነባር ነዋሪዎች  የቅርሱን ባህል እና  እሴትን ለመጠበቅ እየሞከሩ ነው ያሉት ነዋሪው  በጀጎል ከተማ ውስጥ ያሉ አዳዲስ ሰዎች  ስለጀጎል ጥበቃ  ግንዛቤ ኖሯቸው ብዙም አይደሉም  ይህ ደግሞ እንደሚያሳስባቸው አያውቁም።

 በጁጎል ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ የቆሻሻ ብክለት በጥንታዊቷ ከተማ ከባድ ችግር ሆኗል.

 የጀጎል ታሪካዊ ቅርሶች እንዲቆዩ የከተማው አስተዳዳሪዎች ችግሩን በጥሞና እንዲያጤኑት ሀጂ መሀመድ ይመክራሉ።

የሐረሪ ክልል ይህንን የዓለም ቅርስ ለመጠበቅና ለማልማት ህጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።  የቤት እድሳት፣ የውሃ ቁፋሮ እና የመኪና እጥበት አገልግሎት ለጀጎል ግንብ መበላሸት መንስኤዎች ተብለው ተለይተዋል።

የከተማው ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ “ጀጎል ከተቀረጹት ቅርሶቿ ውስጥ አንዱ በመሆኑ ለዩኔስኮ ያለውን ችግር እና የወደፊት ስጋት ሁሉ መደበኛ ባልሆነ መንገድ እሳውቃናል ብለዋል።

 የከተማ አስተዳደሩ ከድርጅቶች እና ከበጎ ፈቃደኛ ዜጎች የገንዘብ እና የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚፈልግ ገልጸው  “የጀጎልን ባህላዊ ደረጃውን ለማስቀጠል የምናደርገውን ጥረት ማገዝ የሚፈልግ  ማንኛውንም ሰው በደስታ እንቀበላለን” ብለዋል አቶ ተወለዳ።

 የባህል ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አበባው አያሌው “በአያያዝ ላይ ከክልሉ ባለስልጣናት ጋር ስንወያይ ቆይተናል፣ በክልሉ የሚካሄደውን እቅድ አቅጣጫ አስቀምጠናል” ብለዋል።

ፕሮፌሰር አበባው አያይዘውም ባለሥልጣኑ በዩኔስኮ የተደነገገውን እና የኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርሶች ከሆኑት  አንዱ  ጀጎልን በመጠበቅ ረገድ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል።  ከዚህ አንፃር የከተማ አስተዳደሩ በባለሥልጣኑ ያቀዳቸውን እነዚህን አቅጣጫዎች ለማስፈጸም ከፍተኛ የቤት ሥራ አለበት ብለዋል ። አስ

No comments

Sorry, the comment form is closed at this time.