በምስራቅ ኦሮሚያ ሸዋ ዞን መተሃራ መዝናኛ ቤት ዉሰጥ ታጣቂዎች በሰነዘሩት ጥቃት 10 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ከ11 በላይ ቆስለዋል

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በምስራቅ ሸዋ ዞን በመተሀራ ከተማ በአልጌ ቀበሌ በፈንታሌ ወረዳ መዝናኛ ቤት ዉስጥ ታጣቂዎች 10 ወጣቶችን ሲገድሉ ከ11 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ዘግበዋል።
ጥቃቱ የተከሰተው ሃሙስ መጋቢት 17 ቀን ሲሆን ታጣቂዎቹ ወጣቶቹ ፑል ይጫወቱበት የነበረውን መዝናኛ ቤት በማወካቸው መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ ተናግረዋል።

የመተሐራ ከተማ አስተዳዳሪ አቶ ፍሬዘር አበራ በበኩላቸው ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች 5 ወጣቶች በጥይት መገደላቸውን እና ሌሎች አምስት ደግሞ ቆስለዋል ብለዋል። ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በመተሐራ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ነው። ቀደም ሲል በአልጌ ቀበሌ መተሐራ ፈንታሌ ወረዳ ተመሳሳይ ጥቃት መፈጸሙን የገለጸው ፍሬዘር የአሁኑ ጥቃት ከተጎጂዎች ማንነት ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው የሀገሪቱ ሬዲዮ ዘግቧል። የኦሮሚያ ፖሊስ እና የክልሉ ልዩ ሃይል አባላት ወንጀለኞች በማሳደድ ላይ መሆናቸውን ገልጿል። አዲስ ስታንዳርድ ለበለጠ መረጃ ፍሬዘርን ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።

No comments

Sorry, the comment form is closed at this time.